ነነዌ

ነነዌአሦር ጥንታዊ ከተማ ነበረ። ፍርስራሹ በጤግሮስ ወንዝ ምሥራቅ ዳርቻ በሞሱል ዙሪያ አሁን አለ።

ነነዌ
(ናይኑዋ)
የታደሰው አዳድ በር ፍርስራሽ
ሥፍራ
ነነዌ is located in መስጴጦምያ
{{{alt}}}
መንግሥትየአሦር መንግሥት
ዘመንከ2380 እስከ 620 ዓክልበ.
ዘመናዊ አገርኢራቅ
ጥንታዊ አገርአሦር

ኦሪት ዘፍጥረት 10፡11 መሠረት የሴም ልጅ አሦርሰናዖር ወጥቶ ነነዌንና ሌሎችን ከተሞች ሠራ። አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ግን ከፊተኛው ቁጥር ከ10፡10 በመውሰድ አድራጊው እንደ ናምሩድ ቆጥረውት፣ ናምሩድ እራሱ ወደ አሦር (ወደ ሀገሩ) ወጥቶ እኚህን ከተሞች እንደ ሠራ ይላሉ። በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ ኒኑስ የነነዌ መስራችና የአሦር መጀመርያ ንጉስ ነበረ።

ነነዌ ከጥንት ጀምሮ ከአሹር ከተማ-አገር ይገዛ ነበር። እንደ አሹር ከ1440 እስከ 1366 ዓክልበ. ድረስ በሚታኒ ይቆጣጠር ነበር። ትልቅ ከተማ ነበረ።

በ775 ዓክልበ. አካባቢ ነቢዩ ዮናስ ወደ ነነዌ ሂዶ የአሦር ሰዎች ወደ ንሥሐ እንዳመጣቸው በመጽሐፈ ዮናስ ይገለጻል። የዮናስ መቃብር የሚባለው የተቀደሠ መስጊድ በነነዌ (የአሁኑ ሞሱል) አካባቢ ይገኝ ነበር፤ በሐምሌ 2006 ዓ.ም. የኢስላማዊ ተዋጊዎች ከ«ኢስላም ግዛት በኢራቅና ሶርያ» ወገን የዮናስን መስጊድ አፈረሱት።

በ713 ዓክልበ. ንጉሥ ሰናክሬም የአሦርን ዋና ከተማ ወደ ነነዌ መለሠው።

ዋቢ መጽሐፍት