መጋቢት ፳፱፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፱ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፬ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፶፯ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፮ ቀናት ይቀራሉ።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎችኮድ አርም
- ፲፰፻፹፰ ዓ/ም - የጥንቷ ሮማ ቄሳር ቀዳማዊ ቴዎዶሲዩስ በአዋጅ ከከለከለው ከ ሺ ፭ መቶ ዓመታት በኋላ ዘመናዊው የኦሊምፒክ ውድድር በአቴና ከተማ ተጀመረ።
- ፲፱፻፵ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሥሩ የሚተዳደር ዓለም አቀፍ የሕዝብ ጤንነት ባለ ሥልጣን ድርጅት - ‘የዓለም ጤንነት ድርጅት’ን ( The World Health Organization (WHO)) መሠረተ።
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በርዋንዳ በጎሳ ልዩነት ላይ የተመሠረተው የእርስ በእርስ ፍጅት፣ የሁቱ ጎሠኞች እስከ ፰ መቶ ሺ የሚሆኑ የቱትሲ ብሔር ተወላጆችን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ታይቶም ተሰምቶም በማያውቅ ሁኔታ ፈጇቸው። የውጭ መንግሥታትን በጉዳዩ ጣልቃ እንዳይገቡ በተጤነ ዕቅድ፣ የርዋንዳ ሠራዊት በዚሁ ዕለት አሥር የቤልጂግ ጸጥታ አስከባሪ ወታደሮችን ገድለዋል።