ጥቅምት ፳፯
(ከጥቅምት 27 የተዛወረ)
ጥቅምት ፳፯ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፶፯ተኛው እና የመፀው ፴፪ተኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፫፻፱ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፰ ቀናት ይቀራሉ።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች
- ፲፱፻፴፯ ዓ.ም. - በአሜሪካ ፕሉቶንዬም ለመጀመሪያ ጊዜ ለቦምብ መሥሪያ ተዘጋጅቶ “ፋት ማን” በመባል የሚታወቀውን በጃፓን ናጋሳኪ ላይ የተጣለውን የአቶም ቦምብ ተሠራበት።
- ፲፱፻፵፱ ዓ.ም. - የግብጽ ፕሬዚደንት ጋማል አብደል ናሰር በወቅቱ በብሪታንያ እና በፈረንሳይ ቁጥጥር ስር የነበረውን የሱዌዝ ቦይ የግብጽ ብሔራዊ ንብረት ሲያደርገው የብሪታንያና የፈረንሳይ ሰራዊቶች በቦዩ አካባቢ ግዛቶች ከግብጽ ሰራዊት ጋር ተዋጉ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞንሮቪያ፣ ሌጎስ እና አክራ ከተማዎች አዲስ የበረራ መሥመር አስመረቀ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - “ሚቸል ኮትስ” (Mitchell Cotts) የተባለው የብሪታንያ ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ከኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር በአዋሽ ሸለቆ የተንዳሆን የጥጥ እርሻ ልማት የስምምነት ውል ለመፈራረም አዲስ አበባ ገቡ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ.ም. - አምቺትካ ደሴት ላይ የአሜሪካ የአቶሚክ ኃይል ድርጅት በምድር ውስጥ “ካኒኪን” በሚል ቅጽል ስም የተሰየመውን ኃይለኛ የሃይድሮጅን ቦምብ በማፈንዳት ፈተሸ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) እና የብሪታኒያ መንግሥት በወሎ ክፍለ-ሀገር የመጋቢ መንገዶችን ማሠሪያ ላይ የሚውል የ ፰ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ውል ተፈራረሙ።
ልደት
ዕለተ ሞት
ዋቢ ምንጮች
- (እንግሊዝኛ) P.R.O., FO 371/154836 - Annual Report from Ethiopia for 1960
- (እንግሊዝኛ) P.R.O., FCO 371/536 Annual Review of 1969
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |
🔥 Top keywords: ዋናው ገጽልዩ:Searchሥርዓተ ነጥቦችአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስኢትዮጵያየአድዋ ጦርነትየአክሱም ሐውልትአበበ ቢቂላዓፄ ቴዎድሮስጀጎል ግንብአማርኛአክሱምላሊበላቅዱስ ያሬድአፈወርቅ ተክሌአውሮፓየጋብቻ ሥነ-ስርዓትአርሰናል የእግር ኳስ ክለብኤችአይቪ2ኛው ዓለማዊ ጦርነትጥሩነሽ ዲባባጥላሁን ገሠሠእርዳታ:ይዞታትግራይ ክልልፕሮቴስታንትዳግማዊ ምኒልክመዝገበ ቃላትየኢትዮጵያ ነገሥታትሐረርዘጠኙ ቅዱሳንየኢትዮጵያ የ5 ሺ ዓመት ታሪክ ከኖኅ እስከ ኢህአዴግውክፔዲያእምስሥነ-ፍጥረትዩ ቱብገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞችአዲስ አበባመጽሐፍ ቅዱስግራኝ አህመድ