ባይ-ዩዕ
ባይ-ዩዕ (ቻይንኛ፦ 百越) ወይም «መቶ ዩዕ» በጥንት (ቢያንስ ከ1200 ዓክልበ.) በደቡብ ቻይና እና ስሜን ቬትናም የተገኙት ብሔሮች ነበሩ።
ባሕል
ባሕላቸው ያንጊዜ ከቻይና ሰዎች ባሕል በጣም እንደ ተለየ ይታወቃል። ከሩዝ በቀር ብዙ እርሻ አላደረጉም፤ በማደንና በተለይ አሣን በማጥመድ ይኖሩ ነበር፤ እንዲሁም የውሃ ጎሽን ለማዳ አደረጉ። ጎጆቻቸውን በምርኩዞች ላይ ይሠሩ ነበር፣ ጸጉራቸውን ያቋርጡና በቆዳቸው ንቅሳት ያድርጉ ነበር፤ ቻይናዎች ግን ያንጊዜ የኮንግ-ፉጸ ተከታዮች ሆነው ጽጉራቸውን አላቋረጡም፣ ንቅሳት አላደረጉምና ስለዚህ የባይ-ዩዕ ሕዝቦችን እንደ አረመኔዎች ያህል ይቆጥሯቸው ነበር። የዩዕ መንግሥታት ግን ጥራት ያለውን መርከብ እና ሠይፍን በመሥራት አንጋፋዎች ሆኑ፤ አገራቸውም በሉል፣ ዕጣን፣ ዝሆን ጥርስ፣ አውራሪስ ቀንድ፣ ኤሊ ዘጎል፣ ዛጎል ድንጋይ፣ ብቅበቃ፣ ጣውስ ዕጅግ ሀብታም ነበረ።
ቋንቋ
ለቋንቋቸው ትንሽ ናሙና ቢኖረን ከዘመናዊ ቋንቋዎች መካከል የትኛውን እንደ መሠለ ስላለው ጥያቄ አንዳንድ ክርክሮች አሉ። እንደ ዘመናዊ ቬትናምኛ እንዳልመሠለ ግልጽ ነው።
ደግሞ ይዩ
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
🔥 Top keywords: ዋናው ገጽልዩ:Searchሥርዓተ ነጥቦችአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስኢትዮጵያየአድዋ ጦርነትየአክሱም ሐውልትአበበ ቢቂላዓፄ ቴዎድሮስጀጎል ግንብአማርኛአክሱምላሊበላቅዱስ ያሬድአፈወርቅ ተክሌአውሮፓየጋብቻ ሥነ-ስርዓትአርሰናል የእግር ኳስ ክለብኤችአይቪ2ኛው ዓለማዊ ጦርነትጥሩነሽ ዲባባጥላሁን ገሠሠእርዳታ:ይዞታትግራይ ክልልፕሮቴስታንትዳግማዊ ምኒልክመዝገበ ቃላትየኢትዮጵያ ነገሥታትሐረርዘጠኙ ቅዱሳንየኢትዮጵያ የ5 ሺ ዓመት ታሪክ ከኖኅ እስከ ኢህአዴግውክፔዲያእምስሥነ-ፍጥረትዩ ቱብገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞችአዲስ አበባመጽሐፍ ቅዱስግራኝ አህመድ