የብርሃን ፍጥነት

የፀሐይ ብርሃን መሬት ለመድረስ 8 ደቂቃ ከ19 ሰኮንድ ይወስዳል
ትክክልኛ ዋጋ = 299,792,458 ሜትር በሰኮንድ
ተቀራራቢ ዋጋ = 300,000 ኪሎሜትር በሰኮንድ

የብርሃን ፍጥነትc ምልከት ሲወከል፣ ለተፈጥሮ ህግጋት ጥናት ከፍተኛ አስተዋጾ ያለው የተፈጥሮ ቋሚ ቁጥር ነው። ብርሃን በቅጽበት ሳይሆን በተወሰነ ፍጥነት እንደሚጓዝ ቀደምት ሳይንቲስቶች የደረሱበት ጉዳይ ነው። የብርሃን ፍጥነት ለብርሃን ብቻ ሳይሆን ለብርሃን ቤተሰብ ለሆኑት ለኮረንቲና ማግኔት ማዕብሎች ያገለግላል። በአሁኑ ዘመን እንደተለካ፣ የብራሃን ፍጥነት በጥልቁ 299,792,458 ሜትር በሰኮንድ[1] ነው። በሌላ አነጋገር አንድ የብርሃን ጨረር ከፀሐይ ተነስቶ መሬት ለመድረስ 8 ደቂቃ ይፈጅበታል ወይም ደግሞ አንድ የብርሃን ጨረር በየአንድ አንዷ ሰከንድ ወደ ሶስት መቶ ሚሊዮን የሚጠጋ ሜትር (300 ሺህ ኪሎ ሜትር) ይጓዛል።