የቂሪሎስ አልፋቤት

የቂርሎስ አልፋቤት በተለይ ስላቪክ ቋንቋዎችን ለመጻፍ የተደረጀ ጽሕፈት አይነት ነው። በተለይ ሩስኛዩክሬንኛቤላሩስኛቡልጋርኛሰርብኛ ወዘተ. ይጻፉበታል።

ታሪክ

ግላጎሊቲክ

በ855 ዓም ቅዱስ ቂርሎስና ቅዱስ ሜቶዲዮስ ወደ ስላቮች በተላኩበት ጊዜ፣ መጽሐፍ ቅዱስን ወዘተ. በስላቭኛ ለመጻፍ ግላጎሊቲክ አልፋቤት የተባለውን ጽሕፈት ፈጠሩ። ይህም በስላቫዊ ብሔሮች ቶሎ ይስፋፋ ጀመር። በዚህ ግላጎሊቲክ ጽሕፈት ውስጥ፣ አብዛኞቹ ፊደላት የግሪክ አልፋቤት ተደረጁ፣ በግሪክኛ ለማይገኙት ድምጾች ግን አንዳንዱ ከዕብራይስጥ፣ አንዱም ከቅብጥኛ እንደ ተበደረ ይመስላል።

የቀድሞ ቂርሎስ አልፋቤት

ከዚህ ትንሽ በኋላ በ878 ዓም ክርስቲያናዊው የፕረስላቭ ስነ-ጽሑፍ ትምህርት ቤት በቡልጋሪያ ተመሠረተ። በዚህ ተቋም ከ885 ዓም ለስላቭኛ ከግላጎሊቲክ የተሻለ የተቀለለ ጽሕፈት፣ የቀድሞው ቂርሎስ አልፋቤት ተፈጠረ። በዚህ ጽሕፈት ፊደሎቹ ከግላጎሊቲክ ይልቅ እንደ ግሪኮቹ ፊደላት ይመሳሰሉ ነበር። በግሪክኛ ለማይገኙት ድምጾች አንዳንድ ግን ከግላጎሊቲክ ተወሰደ። ይህም የቀድሞው ቂርሎስ አልፋቤት በየጥቂቱ በስላቫዊ ብሔሮች መሃል የግላጎሊቲክ አልፋቤትን ፈንታ ተካ።

የቀድሞ ቂርሎስ አልፋቤት፣ 885 ዓም. ግድም (40 ፊደላት) (* = ለግሪክ ወይም ለባዕድ ቃላት ካልሆነ በቀር ብዙ አልታዩም)
ፊደላትабвгдежѕиіклмнопрстоуф*хѡ*цчшщъьѣюѫѭѧѯ*ѱ*ѳ*ѵ*
ድምጽድዝሽትኢውኦኝዮኝኧኝክስፕስኢው

ከዚህ ትንሽ በኋላ ሌሎች የቀድሞ ፊደላት ꙗ /ያ/፣ ѥ /የ/፣ ѩ /የኝ/ ተጨምረው ነበር።

ዘመናዊ ቂርሎስ አልፋቤት

ከጊዜ ወደ ጊዜ የድሮ ቂርሎስ አልፋቤት ለየቋንቋው ተለወጠ፤ በተለይም የሩስያ ጻር ታላቁ ፕዮትር በ1700 ዓም አንዳንድ ለውጥ አስገባ።

ዘመናዊ ቂርሎስ ፊደላት ከ1700 ዓም. በኋላ
ፊደላትабвгдеёжзийклмнопрстуфхцчшщъьэюя
ድምጽሽች

ከነዚህ ጋራ ተራ ፊደላት በላይ፣ እያንዳንዱ ቋንቋ ለራሱ ተጨማሪ ልዩ ፊደሎች አሉት። ለምሳሌ፣ በዩክሬንኛ አልፋቤት «г» የሚለው ፊደል ለ/ሕ/ ያሰማል፣ ሌላውም ቅርጽ «Ґ» ለ/ግ/ ያገልግላል።

ሌሎችም ስላቫዊ ያልሆኑት ልሳናት በተለይም ሞንጎላዊ፣ ቱርኪክ ቋንቋዎች ወይም ሳይቤራዊ ቋንቋዎች ደግሞ በቂርሎስ ጽሕፈት ይጻፋሉ፣ ወይም ቀድሞ በቂርሎስ ጽሕፈት ተጽፈው ነበር።